Uncategorized

በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተገነባው ዘመናዊ የፕላስቲክ ቧንቧና መገጣጠሚያ ማማረቻ ፋብሪካ ሊመረቅ ነው

በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በ14 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር ወጪ የተገነባ ዘመናዊ የፕላስቲክ ቧንቧና መገጣጠሚያ ማማረቻ ፋብሪካ የፊታችን ቅዳሜ ይመረቃል። ፋብሪካውን “ዜድ ኤም ትሬድ እና ኢንቨስትመንት” የተሰኘው ኢትዮጵያዊ የንግድ ኩባንያ እና የቻይናው ዓለም ዓቀፍ ድርጅት ሪፎ በጋራ እንደገነቡት ተገለጿል። የፋብሪካውን ምርቃ አስመልክቶ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና የኩባንያዎቹ ከፍተኛ አመራሮች በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። ፋብሪካው በዘርፉ …

በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተገነባው ዘመናዊ የፕላስቲክ ቧንቧና መገጣጠሚያ ማማረቻ ፋብሪካ ሊመረቅ ነው Read More »

ኮሚሽኑ ባለፉት አራት ወራት 64 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ሰበሰበ

የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት አራት ወራት 64 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 95 በመቶ ማሳካቱን አስታወቀ። ኮሚሽኑ በአራት ወራት የተከናወኑ ሥራዎችን የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል። በገቢ አሰባሰብ፣ ኮንትሮባንድ እና ሕገ- ወጥ ንግድን በመከላከል ረገድ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ናቸው መባሉን የኮሚሽኑ መረጃ አመላክቷል። የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ÷ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ዘመኑን የዋጀ …

ኮሚሽኑ ባለፉት አራት ወራት 64 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ሰበሰበ Read More »

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 11 ኤ350-900 አውሮፕላኖችን ለማዘዝ ከኤር ባስ ጋር ሥምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 11 ኤ350-900 አውሮፕላኖችን ለማዘዝ የሚያስችል የመግባቢያ ሥምምነት ከአውሮፕላን አምራቹ ኤርባስ ጋር ተፈራረመ ሥምምነቱ ተጨማሪ ስድስት አውሮፕላኖችን የመግዛት አማራጭን በውስጡ ያካተተ እንደሆነ ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ምንጭ፦ ኤፍ.ቢ.ሲ

ክልሉ ከ5 ሺህ ቶን በላይ የቅመማ ቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ሶስት ወራት ከ5 ሺህ ቶን በላይ የቅመማ ቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን የክልሉ ቡና ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አስራት መኩሪያ÷ ከ1 ሺህ 300 ቶን በላይ የሻይ ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን አስታውቀዋል። በ2016 ዓ.ም ከ54 ሺህ ቶን በላይ የቅመማ ቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን ጠቅሰው፤ …

ክልሉ ከ5 ሺህ ቶን በላይ የቅመማ ቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ Read More »

የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን ከአውሮፓ የፈጠራ ባለቤትነት ቢሮ ጋር የትብብር ሥምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን እና የአውሮፓ የፈጠራ ባለቤትነት ቢሮ ሦስተኛው ለሁለት ዓመታት የሚቆይ የሥራ ዕቅዳቸው ላይ በትብብር ለመሥራት ተፈራርመዋል። ሥምምነቱ ከፈረንጆቹ 2023 እስከ 2025 የሚቆይ መሆኑ ተገልጿል። ሥምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ወልዱ ይመስል እና የአውሮፓ የፈጠራ ባለቤትነት ቢሮ ፕሬዚዳንት አንቶኒዮ ካምፒኖስ መሆናቸውን ከኢትዮጵያ የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። በመርሐ-ግብሩ …

የአዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን ከአውሮፓ የፈጠራ ባለቤትነት ቢሮ ጋር የትብብር ሥምምነት ተፈራረመ Read More »

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባንጉይ በረራ ጀመረ

የኢትጵያ አየር መንገድ ወደ ሴንትራል አፍሪካ ዋና ከተማ ባንጉይ በረራ ጀምሯል። የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያዴቻ÷ በ2030 ወደ ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት ዋና ከተሞች የመብረር እቅድ መኖሩን አንስተዋል። አየር መንገዱ በተለያዩ የዓለም ሀገራት የበረራ መዳረሻዎችን እያሰፋና የአውሮፕላን ቁጥሮችንም እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል። በዛሬው ዕለትም ወደ ሴንትራል አፍሪካ ባንጉይ የጀመረው በረራ በአፍሪካ የበረራ መዳረሻዎቹን ወደ …

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባንጉይ በረራ ጀመረ Read More »