Uncategorized

ቻይና በዓለም አቀፍ የመርከብ ግንባታ ዘርፍ ቀዳሚነቷን አረጋገጠች

ቻይና በዓለም አቀፍ የመርከብ ግንባታ ዘርፍ ለ14 ተከታታይ ዓመታት በቀዳሚነት መቀጠሏ ተገለጸ። ቻይና ባለፈው ዓመት ውስጥ በምርታማነት፣ በአዳዲስ ትዕዛዞች እና ቀደም ብለው በተሰጡ ትዕዛዞች ጠንካራ እድገት እያሳየች መምጣቷን አስመስክራለች ተብሏል። በእነዚህ ሦስት ዋና ዋና አመላካቾችም በዓለም አቀፍ የመርከብ ግንባታ ገበያ ውስጥ ለ14 ተከታታይ ዓመታት የመሪነቱን ሥፍራ መያዟን የኢንዱስትሪ እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያወጣው መረጃ ያሳያል። …

ቻይና በዓለም አቀፍ የመርከብ ግንባታ ዘርፍ ቀዳሚነቷን አረጋገጠች Read More »

ኢትዮጵያና ጀርመን በልማት ትብብር ረገድ ያላቸውን ግንኙነት የሚያጠናክር ምክክር አካሄዱ

ኢትዮጵያና ጀርመን በልማት፣ በቴክኒክ እና ምጣኔ ሀብት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር ምክክር አካሄዱ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በጀርመን ውጭ ጉዳይ ቢሮ የፖለቲካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል እና የሊቢያ ልዩ መልዕክተኛ ከሆኑት ክርስትያን በክ (ዶ/ር) ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙርያ መክረዋል። በዚህ ወቅት አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ኢትዮጵያና ጀርመን በልማትና በቴክኒክ ትብብር እንዲሁም በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ …

ኢትዮጵያና ጀርመን በልማት ትብብር ረገድ ያላቸውን ግንኙነት የሚያጠናክር ምክክር አካሄዱ Read More »

በመዲናዋ ለ562 ታማኝ ግብር ከፋዮች እውቅና ተሰጠ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ግብር በታማኝነት ለከፈሉ ግብር ከፋዮች የዕውቅና እና ሽልማት መርሐ ግብር አካሂዷል። በመርሐ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ እና የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አደም ኑሪን ጨምሮ ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። ተሸላሚዎቹ በ2015 በጀት ዓመት ግብርን በታማኝነት በመክፈልና የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ ለከተማዋ ዕድገት እስተዋፅኦ ያበረከቱ …

በመዲናዋ ለ562 ታማኝ ግብር ከፋዮች እውቅና ተሰጠ Read More »

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለኢንዱስትሪ ልማት በቂ የሰው ሀይል እንዳለው ተገለፀ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለኢንዱስትሪ ልማት የሚሆን በቂ የሰው ሀይልና የከተሜነት ምጣኔ አለው ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው ተናገሩ። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አዲሱ የአምራች ኢንዱስትሪ ፖሊሲ እና የተኪ ምርት ስትራቴጂ ዙሪያ በሆሳዕና ከተማ  ውይይት እየተካሄደ ነው። በውይይቱ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው÷ የኢንዱስትሪ ፖሊሲና የተኪ ምርት ስትራቴጂ ጉዳዮች ለክልሉ እድገት …

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለኢንዱስትሪ ልማት በቂ የሰው ሀይል እንዳለው ተገለፀ Read More »

ክልሉ ከ11 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሐብቶች ፈቃድ ሰጠ

በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት 11 ቢሊየን 490 ሚሊየን 458 ሺህ 249 ብር ላስመዘገቡ ባለሐብቶች ፈቃድ መስጠቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል አስታወቀ። ፈቃዱ የተሰጠው በ26 የግብርና እና በሰባት የኢንዱስትሪ ዘርፎች መሆኑን የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገቡም ለ621 ዜጎች ቋሚ የሥራ …

ክልሉ ከ11 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሐብቶች ፈቃድ ሰጠ Read More »

ኮርፖሬሽኑ ከ11 የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ጋር ለመስራት ተስማማ

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከ11 የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ጋር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ። ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ እና ባለሀብቶች ተፈራርመዋል። ባለሃብቶቹ ኮርፖሬሽኑ ካሉት ኢንዱስትሪ ፓርኮች መካከል በአምስቱ የተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ ገብተው ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ነው የተፈራረሙት። በዚህም በመቀሌ፣ ጅማ እና ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በእያንዳንዳቸው ሶስት ሶስት ኩባንያዎች የሚገቡ …

ኮርፖሬሽኑ ከ11 የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ጋር ለመስራት ተስማማ Read More »

ከ100 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት ካስመዘገቡ ኢንቨስተሮች ጋር የውል ስምምነት ተፈረመ

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከ100 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት ካስመዘገቡ ኢንቨስተሮች ጋር የውል ስምምነት ተፈራርሟል። የውል ስምምነት የፊርማ ስነ-ስርዓቱ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አክሊሉ ታደሰ እና ባለሀብቶቹ መካከል እየተከናወነ እንደሚገኝ የኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት ለ10 ቀናት ተራዘመ

የንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት ለቀጣዮቹ አሥር ቀናት መራዘሙን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። በሲስተም መቆራረጥ እና ከክልሎች አወቃቀር ጋር በተያያዘ የንግድ ፈቃድ እድሳት ሂደቱ በመስተጓጎሉ ለሚቀጥሉት አሥር ቀናት ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱንም ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው። አጋጣሚው ነጋዴዎች የንግድ ሥራ ፈቃድ እድሳት አገልግሎትን ያለ ቅጣት ማግኘት የሚችሉበት መሆኑም ተገልጿል። ምንጭ፦ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር

የቻይናዋ ሀርቢን ከበዓል ሰሞን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ከ800 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷ ተነገረ

የቻይናዋ ሀርቢን ከፈረንጆቹ አዲስ ዓመት በዓል ሰሞን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ከ800 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ። በሰሜን ምሥራቅ ቻይና ሄይሎንግጂያንግ ግዛት የምትገኘዋ ከተማ ይህን ያህል ገቢ የሰበሰበችው በሦስት ቀናት የአዲስ ዓመት በዓል የቱሪዝም ዘርፍ ዝግጅት መሆኑ ተጠቁሟል። ከተማዋን የተጨናነቀ የቱሪስት መናኸሪያ ያደረጋት የክረምት የበረዶ ግግሯ፣ ከበረዶ የተሠሩ ቅርፃ ቅርፆቿ፣ የተለያዩ የክረምት ስፖርታዊ ዝግጅቶች …

የቻይናዋ ሀርቢን ከበዓል ሰሞን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ከ800 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷ ተነገረ Read More »

የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ አገልግሎት ጀመረ።

በዚህም አየር መንገዱ በአፍሪካ ያሉትን የጭነት መዳረሻዎች ብዛት ወደ 35 አሳድጓል። አዲሱን በረራ አስመልክቶ የኢትዮጵ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ አገልግሎት መስጠት በመጀመራችን ታላቅ ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል የኢትዮጵ አየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው። ይህ በረራ የሰሜን አፍሪካን የመግሪብ ቀጠና ወደ …

የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ አገልግሎት ጀመረ። Read More »