OneStop

የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሺየቲቭ ለድህነት ቅነሳ አስተዋፅኦ ማድረጉን ቻይና ገለጸች::

“ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አለም ዓቀፉ የቻይና ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሺየቲቭ በዓለም ላይ ድህነትን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ አስተዋጽኦ ማድረጉን የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስተቴር አስታወቀ። የቻይና የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ማኦ ኒንግ፤ “ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ” የተባለው የቻይና ትብብር ለድህነት ቅነሳ ፕሮገራም ያደረገውን አስተዋፅኦ በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም የ2013 ዘላቂ ልማት …

የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሺየቲቭ ለድህነት ቅነሳ አስተዋፅኦ ማድረጉን ቻይና ገለጸች:: Read More »

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም መክፈቻ መርሃ ግብር ላይ ንግግር አደረጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም መክፈቻ መርሃ ግብር ላይ ንግግር አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የቻይና-አፍሪካን ግንኙነት ጥንተ መሰረት እና እድገት አውስተው በቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ (BRI) የመሰረተ ልማት ክንውን በአፍሪካ አህጉር የተጣለውን ጠንካራ የትብብር መሰረትም አንስተዋል። በማደግ ላይ ያለውን የአፍሪካን ተፅእኖ የመፍጠር አቅም አፅንዖት በመስጠትም በባለ ብዙ ወገን መድረኮች አካታችነትን ማረጋገጥ …

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም መክፈቻ መርሃ ግብር ላይ ንግግር አደረጉ Read More »

ምክር ቤቱ የዲፕሎማቲክና ሰርቪስ ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት የሚያግዙ አዋጆችን አጸደቀ

በኢትዮጵያ እና ደቡብ ኮሪያ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በህንድ ሪፐብሊክ መንግስታት መካከል የዲፕሎማቲክና ሰርቪስ ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛ ለማስቀረት የተደረገውን ስምምነት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አጸደቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው በኢትዮጵያ እና በደቡብ ኮሪያ እንዲሁም በህንድ ሪፐብሊክ መንግስታት መካከል የዲፕሎማቲክ እና ሰርቪስ ፓስፖርት ለያዙ …

ምክር ቤቱ የዲፕሎማቲክና ሰርቪስ ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት የሚያግዙ አዋጆችን አጸደቀ Read More »

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከሶስት የቻይና ኩባንያዎች ጋር የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከሶስት የቻይና ኩባንያዎች ጋር የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ። ስምምነቱን የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ከኩባንያዎቹ የሥራ ሃላፊዎች ጋር ተፈራርመውታል። ስምምነቱ ከሁለት ፋርማሲዩቲካል እና አንድ በግብርና ማቀነባበር ዘርፍ ከተሰማራ ኩባንያ ጋር የተፈረመ መሆኑን ኮሚሽነሯ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል። በስምምነቱ መሰረት ኩባንያዎቹ በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ዘርፎች የሚሰማሩ ሲሆን፣ ይህም ለኢኮኖሚው ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ኮሚሽነሯ አስታውቀዋል። ምንጭ፦ …

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከሶስት የቻይና ኩባንያዎች ጋር የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ። Read More »

ሺ ጂንፒንግ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የግሪን ቤልት እና ሮድ አካል ሆኖ ሊደገፍ እንደሚችል አረጋገጡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ከየልዑካን ቡድናቸው ጋር በመሆን በቻይና ታላቁ የሕዝብ አዳራሽ የሁለትዮሽ ውይይት አደረጉ። በውይይታቸውም÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የቻይና ኢንቨስትመንት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እመርታ የሚኖረውን አስተዋፅዖ አንስተዋል። አክለውም በተለይም በአምስቱ ቁልፍ ምሰሶዎች ማለትም÷ በግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ አይሲቲ፣ ማእድን ልማት እና ቱሪዝም ላይ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት እንዲኖር የማበረታቻ ጥሪ አቅርበዋል። ፕሬዚዳንት …

ሺ ጂንፒንግ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የግሪን ቤልት እና ሮድ አካል ሆኖ ሊደገፍ እንደሚችል አረጋገጡ Read More »

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኬ ያንግ ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸው ወቅትም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የምጣኔ ኃብት ትብብር ግንኙነት ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመንግስታቸውን ባለብዙ ዘርፍ የእድገት አላማ ብሎም የተገኙ ድሎችን በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል። በተጨማሪም ከቻይና ጋር የንግድ ግንኙነቶችን …

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ Read More »

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ቻይና ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ቻይና ቤጂንግ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቆይታቸው ከሚኒስትሮች ልኡኮቻቸው ጋር በመሆን በ3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ ፎረም ላይም እንደሚሳተፉ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል። ምንጭ፦ ኤፍ.ቢ.ሲ