
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በኬኒያ በተካሄደው የ2025 የአየር ዕቃ ጭነት አገልግሎት ልሕቀት ሽልማት መርሐ-ግብር “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” በመባል ዕውቅና ተቀዳጀ።
በተጨማሪም “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት ኤርፖርት” እና “ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ያለ የዓመቱ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” በመባል ተደራራቢ ዕውቅና እና ሽልማት ማግኘቱን አየር መንገዱ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል።
እነዚህ ሽልማቶች የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ላለው ዘርፈ ብዙ ዓለም አቀፍ አገልግሎቶች አስተማማኝነትና ቅልጥፍና ማረጋገጫዎች ናቸው ብሏል ተቋሙ።
የበረራ አድማሳችንን እና አገልግሎታችንን በማጠናከር አህጉራዊ መሪነታችንን እና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነታችንን ለማስቀጠል በዕጅጉ የሚረዱ ናቸው ሲልም ገልጿል።
ምንጭ፦ ኤፍ.ኤም.ሲ